Sunday, April 6, 2014

የደሴው ሰላማዊ ሰልፍ በድምቀት ተካሄደ! (ከተጨማሪ ፎቶዎች ጋር)

የደሴው ሰላማዊ ሰልፍ በድምቀት ተካሄደ! (ከተጨማሪ ፎቶዎች ጋር)

(EMF) ዛሬ መጋቢት 28 ቀን በደሴ የሚደረገውን ሰላማዊ ሰልፍ ያስተባበረው አንድነት ፓርቲ ነው:: የፓርቲው ከፍተኛ አመራር አባላት በትላንትናው እለት ቅስቀሳ እያደረጉ በነበረበት ወቅት ፖሊስ እና ደህንነቶች ቅስቀሳውን ለማስቆም ጥረት አድርገው ነበር:: በተለለይም የከተማው የጸጥታ ዘርፍ ሃላፊ ነው የተባለው ሰው የቅስቀሳ መሳሪያዎችን ጭምር ለመንጠቅ ሙከራ አድርጎ ነበር – ባይሳካለትም::
ይህ ሁሉ አልፎ ዛሬ ህዝቡ በነቂስ ወጥቶ በአስተዳደሩ ላይ በተለይም በመሬት ይዞታ ባለቤትነት ጉዳይ እና አላግባብ ስለታሰሩት ኢትዮጵያውያን ድምጹን ከፍ አድርጎ እያሰማ ይገኛል:: ሰላማዊ ሰልፉ እንደተጀመረ ፖሊስ መንገዱን በመዝጋት ሰልፈኛውን ለማወክ ጥረት አድርጎ ነበር:: ህዝቡ ግን ፖሊስን እየጣሰ ሰልፉን በሰላማዊ መንገድ እያደረገ ነው::
dessei11

በሰልፉ ላይ…
-ዜጎችን ከቀያቸው ማፈናቀል ይቁም
- መሬት ለህዝብ ይመለስ
- ጭቆና በቃን
- ድል የህዝብ ነው
- በግፍ የታሰሩ ይፈቱ
- መሬት ከካድሬው ወደ ህዝቡ ይመለስ
- አንድነት ኃይል ነው
- የፖለቲካ እስረኞች ይፈቱ… የሚሉ መፈክሮች ሲስተጋቡ ነበር::
ለተሰበሰበውም ህዝብ በደሴ የአንድነት ተወካይ በቅድሚያ ንግግር አድርገዋል:: ኢንጂነር ዘለቀ ረዲ እና የአንድነት ፓርቲ ምክትል ፕሬዘዳንት አቶ ተክሌ በቀለ ንግግር አድርገው ሰላማዊ ሰልፉ በኢትዮጵያዊ ጨዋነት ተጠናቋል:: የደሴም ህዝብ ብሶቱን የሚያሰማበት መድረክ በመፈጠሩ ምስጋናውን ለፓርቲው አመራሮች አቅርቧል::
ተጨማሪ ፎቶዎችን ከፓርቲው ምንጮች ስናገኝ በርከት አድርገን እናቀርባለን!
Share Button

No comments:

Post a Comment