Friday, November 15, 2013

የሞ ኢብራሂም ፋውንዴሽንና የአፍሪካ አንባገነን መሪዎች

(Mo Farah Foundation and Africa’s dictatorial leaders )
(ዘንድሮስ ተሸላሚ ያገኝ ይሆን ወይ?)

Thewodros Getachew
November 9, 2013                                                                       

በአፍሪካ መዲናዋ አዲስ አበባ ከጥቂት ወራት በፊት የሞ ኢብራሂም ፋውንዴሽን ኮንፈረንስ አዘጋጅቶ የነበረ ሲሆን ኮንፈረንሱ አፍሪካ  ውስጥ ስላለው የመልካም አስተዳደርና ዲሞክራሲ በተመለከተ እንዲሁም አህጉሪቷ ወደፊት ስለሚኖሩዋት  እድሎችና ስላጋጠሙዋት ችግሮች ከተለያዩ ሃገራት ከመጡ ፖለቲከኞ፤ ታዋቂ ግለሰቦችንና ጋዜጠኖችን ጨምሮ የተካሄደ ነበር።                                                                                                                                                                                                                                                                       
በዛን ኮንፈረንስ ላይ ከዋንኟዎቹ ተናጋሪዋች ውስጥ የነበሩት አደራ ጠባቂው / ሚኒስትር ሐይለማርያም ደሳለኝ ኢትዮጵያ ውስጥ ስለሰፈነው አስገራሚ ዲሞክራሲና እድገት የተለመደውንና ማቆሚያ ያልተገኝለትን የመንግስታቸውን ቅጥፈት ለማስተጋባት ተጠቅመውበታል።  ይሁንና ኢትዮጵያ ውስጥ ዲሞክራሲ እንደሳቸው አባባል ሞልቶ ከተረፈ እንዴት ከ90 ሚሊዮን ህዝብና 90 ምናምን ፓርቲ በላይ እንዳለ በሚነገርባት ሃገር ውስጥ አንድ ፓርቲ ብቻ በአንባገነንነት ሃገሪቷን በሞኖፖል ለ 23 አመታት ሊገዛ እንደቻለ  ወይም የሃገሪቷ ፓርላማን 99.6% ከአንድ ፓርቲ ብቻ  የተወጣጣ አባላትን ይዞ የፓርቲ ጉባኤ እንደመሰለ ግን ሊያስረዱ አልቻሉም ነበር
በርግጥ ይሄ ባጠቃላይ የአገዛዙ ባህሪ መሆኑ የታወቀ ነው በትክክል ከእውነታው ጋር የተጋጨ ወይንም መረጃዎቹን   አዛብቶ ፤አባዝቶ፤ ቀንሶ፤ ጨምሮ የተሳሳተ/distorted  አድርጐ ማቅረብ  የተለመደና የስርአቱ አንድ አካል የሆነ እውነት ነው።

ሃገሪቷ ውስጥ በየቦታው  በአገዛዙ የሚፈጸመው  የሰብእዊ መብት ጥሰት፤ በየእስር ቤቱ ታጉረው የሚገኙት ጋዜጠኞችና የፖለቲካ እስረኟች እንዲሁም የፍትህ ስርእቱ የመንግስት እና የግብረአበሮቹ የማጥቂያ መሳሪያ መሆንና ስር የሰደደው ሙስና ሌሎችም በርካታ  ምክንያቶች ኢትዮጵያ በአሁኑ ሰአት በየትኛውም መለኪያ የመልካም  አስተዳደርና የዲሞክራሲ ምሳሌ ለመሆን አያስችላትም አለመሆንም ብቻ ሳይሆን  ወደዛ የሚደረገውን ጉዞ ገና አልጀመረችም፤  በተለያየ ግዜ ዲሞክራሲ እና መልካም አስተዳደር ልትጀምርባቸው የምትችልባቸው ወርቃማ  አጋጣሚዎች ደግሞ በአንባገነኖች ጥቂት ለማይባሉ ግዜዎች ከሽፈዋል።








                                                                                                                                                                                          ለማንኛውም ሱዳን ውስጥ እንደ ፈረንጆቹ አቆጣጠር  1946 የተወለደው / መሃመድ ሞህ ኢብራሂም የሱዳን ብሪቲሽ የሞባይል ቴሌኮምንኬሽን ባለቤትና ሴልቴል/ celtel የተባለው ድርጅት መስራችና ባለቤት የነበረ  ሲሆን 2005 ድርጅቱን 3.4 ቢሊዮን ብር ከሽጠ በሓላ የሞ ኢብራሂም ፋውንዴሽን   አፍሪካ ውስጥ መልካም አስተዳደርን ለማበረታታት በሚል  እንዲሁም  ጎን ለጎን ደሞ የየሃገሮቹን የመልካም አስተዳደር ብቃት ደርጃ የሚለካና የሚገመግም  Mo Ibrahim index  የሚባል ድርጅት በዚሁ ግለሰብ እማካኝነት ተቋቍሞ  2007 ጀምሮ  የመልካም አስተዳደር መስፈርት ላሟሉ መሪዋች የመነሻ ሸልማት 5 ሚልዮን የአሜሪካ ዶላር አንዲሁም በየአመቱ  አስከ ህይወታቸው መጨረሻ ድረስ 200 የአሜሪካ ዶላር  ለነዚሁ ሃገራቸው ውስጥ  መልካም አስተዳደረንና ፤ዲምክራሲን፤ ሰላም ላሰፈኑ  መሪዋች እያበረከት ይገኛል ። 
          
            
      Dr. Mohamed “Mo” Ibrahim (born 1946

2007 አንደ ፈረንጆቹ አቆጣጠር የተመሰረተ ፋውንዴሽን በየአመቱ ከአፍሪካ መሪዎች መካከል በመልካም አስተዳደር በዲምክራሲ በሰላም በፍትሕ አንዲሁም በኢኮኖሚ ሃገራቸው ውስጥ ለውጥ ያመጡ  በሰላም አና በህገመንግስቱ መሰረት ስልጣን የለቀቁ ወይም ያስረከቡ መሪዎችን   ለመሸለም እንዲሁም  ለማወደስ ተብሎ የተቐቐመ ድርጅት ነው።
       
በየአመቱ በሚሊዮን የሚቆጠር  የአሜሪካ ዶላር መድቦ መልካሙን የአፍሪካ መሪና አስተዳዳሪ ለመሸለም  ተዘጋጅቶ የሚጠበቀው ፋውንዴሸን መልካም መሪዋችን የመለየት ሳይሆን የማግኝት ከባድ ፈተና አንደገጠመው ለማወቅ ከተመሰረተበ ግዜ ጀምሮ ለመሸለም የበቁት የአፍሪካ መሪዎች ኔልሰን ማንዴላን ሳይጨምር ሶስት ብቻ መሆናቸው ማወቅ  ብቻ ይበቃል።
     
ፋውንዴሽኑ በተቋቋመበት አመት ማለትም 2007 አንደ ፈረንጆቹ አቆጣጠር  የመጀምሪያውን ሽልማት ለማግኝት የበቁት የሞዛምቢኩ መሪ ቺሳኖ ለሽልማት ያበቃቸው አገራቸው ውስት ባመጡት ሰላምና ብሄራዊ አርቅ አንዲሁም ዲሞክራሲና መረጋጋት ከኢኮኖሚያዊ አድገት ጋር የሽልማቱ ተቋዳሽ አንዲሆኑ አስችሎዋቸዋል።
    president Joaquim Alberto Chissano                                                                                                    
በ 2008 ደሞ የቦትስዋናው መሪ ሞጋኢ ፪ ኛውን ሽልማት ባገራቸው ውስጥ ባመጡት ሰላምና መረጋጋት አንዲሁም በ ኤችአይቪ ኤድስ ላይ ባስመዘገቡት ስኬት ሽልማቱን ተረክበዋል።


President Festus Gontebanye Mogae, Botswana             

2009 አና 2010 ግን ፋውንዴሽኑ ተሸላሚ መሪ ከአፍሪካ ምድር ማግኝት ሳይቻለው ቀርቶዋል በመሆኑም ለሸልማቱ አዘጋጅቶት የነበረዋን ገንዘብ ወደ ካዝናው መልሶታል
2011 ግን አፍሪካ ውስጥ በአግር በፈረስ ሲያስፈልግ የነበርው መልካም የአገር አስተዳዳሪ ከወደ ኬብቨርዲ ተገኝቶዋል ፕሬዝዳንት ፔድሮ  ቨሮና አገራቸውን ወደ ሞዴል ዲምክራሲ ከሚባሉት የአፍሪካ አገራት ተርታ በማሰለፋቸው ሽልማቱን ወደ ቤታቸውና ወደ አገራቸው ለማስገባት በቅተዋል


President Pedro de Verona Rodrigues Pires, Cape Verde
      

የም ኢብራሂም ፋውንዴሽን በሚሊዮን  ዶላር የለጠፈበት የመልካም አስተዳዳሪ መሪ ሽልማት አመት ውስጥ ማግኝት የቻለው     በስልጣን ላይ ያሉ መሪዋች አነዚሁ ብቻ ነበሩ
     
2011 በኸዋላ ግን ተሸላሚ ሳያገኝ ወደ 2014 አየሄደ ነው ዘንድሮም ተሸላሚ ማግኝት ባልመቻሉ የሚሸልሙት መሪ ባይገኙ የሚሸልሙት ቡድን ለማግኝት ይመስላል ይሄንን የአግር ዃስ    ውድ ድር ያዘጋጁት
         
ከአንድ ቢሊዮን ህዝብ በላይ ያላት  አፍሪካ 61 አገራትን ያካተተ  አህጉር የሚመሩ 61 መሪዋች መካከል አንድ አንኳን ለዚህ ሸልማት የሚበቃ መሪ ማግኝት አለመቻል ከባድ ሃዘን ላይ የሚጥል አሳፋሪ ክስተት ነው http://listofafricancountries.com/
         
አለም በሌላኛው ጫፍ በዲምክራሲ አና በሰባአዊ መብት መክበር ሲከንፍ ጉደኛዋ አፍሪካ ደም በብዙ እርቀት ከነዚንህ እሴቶች በተቃራኒው  አየራቀች ትገኛለች አፍሪካ ውስጥ አገሮቹን የሚመሩ መሪዋች ስልጣን ላይ ተጣብቀው ያለምንም ይሉኝታ 21 ክፍለዘመን በፍጽም አንባፈነናዊ  አገዛዝ ይሄንን ግዙፍ አህጉር ህዝብ አያንገላቱትና አያላጉት ይገኛሉ

በተለይም ደሞ በአፍሪካው ቀንድ ከአንዱ የእርስ በእርስ ጦርነት ወደ ሌላው ከአንዱ አንባገነን ወደ ሌላውኛው  እየተሸጋገረ ዜጎችም ጦርነቱንና የአንባገነኖችን ዱላ በመሸሽ በመላው አለም ላይ አንደ አሸዋ ተበትነው ይገኛሉ በዚህ ሂደት ላይ ግን በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች ህይወታቸውን አጥተዋል። 

በተለይም ደግሞ የአፍሪካው ቀንድ ከአንዱ የእርስ በእርስ ጦርነት ወደ ሌላው ከአንዱ አንባገነን ወደ ሌላውኛው  እየተሸጋገረ ዜጎችም ጦርነቱንና የአምባገነኖችን ዱላ በመሸሽ በመላው አለም ላይ አንደ አሸዋ መበተን ግድ ብሎዋቸዋል  በዚህ ሂደትም  በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች ህይወታቸውን አጥተዋል። ኢትዮጵያም ምንም እንኳን ከቅኝ  አገዛዝ ቀንበር ራሷን ጠብቃ መቆየት ከመቻልዋም  በላይ ለሌሎች የአፍሪካ አገሮች ነጻነታቸውን አንዲያገኙ ከፍተኛ እገዛ በማድረግ የጥቁር ህዝቦች ኩራት ለመሆን ብትበቃም ዲሞክራሲና መልካም አስተዳደርን በሃገራ በማስፈን ምሳሌ መሆን አልቻለችም በመሆኑም የአጉሪቷ ጭራ ሆና በማዝገም ላይ ትገኛለች።


የሞ ኢብራሂም ፋውንዴሽን ደሞ ይሄንን አስከፊ እውነታ በግልጽ እንዲታይ አንድ ምክንያትና ምልክት ሆናል።  በርግጥ በአፍሪካ ውስጥ ዲሞክራሲና መልካም አስተዳደር ያሰፈኑ ጥቂት ሃገሮች ቢኖሩም አህጉሪታ በአብዛኛው በዲሞክራሲ በመልካም አስተዳደር አጦት ጨለማ አደወረሳት ወደኍላ መንሸራተትዋን ተያይዛዋለች።
      

No comments:

Post a Comment